ዛሬ ማለዳም የእስራኤል የአየር ኃይል ጀት የኢራንን አምስት የጦር ሄሊኮፕተሮች ለይቶ ማጥቃቱን ተናግረዋል። ቃል አቀባዩ እንደተናገሩት ሄሊኮፕተሮቹ የእስራኤልን አውሮፕላኖች ለማጥቃት ያለሙ ነበሩ። የኢራን ባለሥልጣናት በበኩላቸው በሁለቱ ሃገራት ግጭት ውስጥ አሜሪካ ጣልቃ ሳትገባ እንዳልቀረች እየተናገሩ ነው።