በአዲስ አበባ ከተማ የትግራይ ተወላጀች ላይ ያነጣጠረ የዘፈቀደ እስር እየተፈፀመ ነው ሲል ቅድሚያ ለሰብአዊ መብቶች የተባለ አገር በቀል የመብቶች ድርጅት አመለከተ፡፡ ሰብዓዊ ድርጅቱ ትናንት ሰኞ ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም. በይፋ ባወጣው ሪፖርት የጅምላ እስር ያሉት ተግባሩ በበራካታ የመዲናዋ ፖሊስ ጣቢዎች ላይ መታየቱን አስረድቷል፡፡