ኢትዮጵያ ውስጥ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባን ጨምሮ አሽከርካሪዎች በነዳጅ እጥረት በብርቱ መፈተናቸውን እየገለጹ ነው። ማደያዎች ነዳጅን በሕገወጥ እያወጡ ዋጋን ጨምረው መሸጥና ወር እየተገባደደ በመጣ ቁጥር ጭማሪ ይደረጋል በሚል ምርቱን መደበቅ መዘዝ እያስከተለ ነው ተብሏል።