ፖላንድ ሕገ-ወጥ ስደትን ለመከላከል ኢትዮጵያ እና ኤርትራን ጨምሮ በስድስት ሀገራት ዘመቻ መጀመሯን አስታወቀች። የፖላንድ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ራዶስላው ሲኮርስኪ በኤክስ ባጋሩት ቪዲዮ በሕገ-ወጥ መንገድ ድንበር ያቋረጠ ሰው ጥገኝነት እንደማይሰጠው ያስጠነቅቃል። በዘመቻው ሶማሊያ እና ግብጽ ጭምር መካተታቸውን ውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።