የህክምና ዋስትና የሌላቸዉ በደቡብ አፍሪቃ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ለመዉለድ ሆስፒታል የሄዱ ነፍሰጡር እህቶቻችን፤ ዘመዶቻችን በመጤ ጠል ሆስፒታል እንዳይገቡ ተከለከሉ ሲሉ አማረሩ። በደርባን ከተማ ሆስፒታል በራፍ ላይ ለመግባት የሞከሩት ነፍሰጡሮች በመከልከላቸዉ የተቆጡ ከአስር የሚበልጡ ኢትዮጵያዉያን በፖሊስ በተተኮሰ የጎማ ጥይት ቆሰለዋል።