ሩሲያ በዩክሬን የጀመረችው ጦርነት ዛሬ ሰኞ 68ኛ ቀኑን አስቆጥሯል። ብርቱ ሰብዓዊ፣ ኤኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ቀውስ ያስከተለው ጦርነት ሰሞኑን ወደ ነዳጅ ግብይት የመሻገር አዝማሚያ እያሳየ ነው። ሩሲያ ለፖላንድ እና ቡልጋሪያ የምታቀርበውን ነዳጅ በሩብል ለመክፈል ፈቃደኛ አልሆኑም በሚል ምክንያት አቋርጣለች። የአውሮፓ ኅብረት ውሳኔውን ነቅፏል