ከኢትዮጵያ የ2019 መደበኛ በጀት ውስጥ 43.8% ወይም 542 ቢሊዮን ብር ለዕዳ ክፍያ ተመድቧል። ብድር መክፈል ያቃታቸው ሁለት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች የውጭ ዕዳ ክፍያ በበጀቱ ውስጥ ተካቷል። ለበቅርቡ የሥራ ጊዜውን ለሚያጠናቅቀው ሕግ አውጪ ምክር ቤት የቀረበው የ2.34 ትሪሊዮን ብር በጀት ከ300 ቢሊዮን ብር በላይ ጉድለት ይገጥመዋል።