ባለፉት ሁለት ዓመታት ገደማ በስራ ላይ የነበረው ኮሚሽኑ በአንድ በኩል ሀገሪቱ ካለችበት ግጭት እና ጦርነቶች የተነሳ ሃገራዊ ምክክሩን አላፈጠጠነም የሚል ቅሬታ ሲቀርብበት በሌላ በኩል ደግሞ ለገዢው ፓርቲ የወገነ እና ሌሎች ባለድርሻ ሊሆኑ የሚገባቸውን ተቃዋሚ ፓርቲዎች እና ታጣቆዎችን አላካተተም በሚል የአካታችነት ጥያቄ ሲነሳበት ይሰማል።