የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በልዩ ልዩ ፖለትካዊ ምክንያቶች በእሥር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ከእሥር ሊለቀቁ የሚችሉበት ዕድል ስለመኖሩ ፍንጭ ሰጡ። መንግሥታቸው "የሃይማኖት አባቶችን እና ትልልቅ ሰዎችን" ተጠቅሞ "በተቻለ መጠን በእሥር ላይ ያሉ ሰዎችን ለመፍታት" ፍላጎት እንዳለው ጠቁመዋል ።