የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ጋር “ዘላቂ የሰላም ሥምምነት” ተፈራረሙ መባሉን የድርጅቱ መሪ አቶ እስክንድር ነጋ ውድቅ አደረጉ። አቶ እስክንድር ነጋ ዛሬ ለዶቼ ቬለ እንዳሉት ድርጅታቸው ከመንግስት ጋር «አልተደራደረም» ፤ «የመደራደር ፍላጎትም የለውም»።