በእስር ላይ የሚገኙ አምስት ጋዜጠኞችን የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት እንዲፈቱ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች በድጋሚ ጥሪ አቀረበ። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን መንግሥት ከ600 በላይ እስረኞች መፍታቱን ቢያስታውቅም ጋዜጠኞቹ ጎበዜ ሲሳይ፣ መስከረም አበራ፣ ገነት አስማማው አስማማው፣ ዳዊት በጋሻው እና አባይ ዘውዱ አሁንም እስር ቤት ናቸው።