ኢትዮጵያውያን የተሻለ የሥራ እና የገቢ አማራጭ ፍለጋ ወደ አረብ ሀገራት፣ ደቡብ አፍሪካ እና በሰሐራ በኩል ወደ አውሮፓ ሲጓዙ ለሞት፣ ስቃይ እና እንግልት ይዳረጋሉ። ዜናውን የሰሙ አለፍ ሲልም ሰቆቃውን የሚያውቁ ከመሰደድ አልተቆጠቡም። ተማራማሪዎች በኢትዮጵያ “ስደት እንደ አማራጭ ሳይሆን እንደ ብቸኛ መፍትሔ እየተቆጠረ” መምጣቱን ይናገራሉ።