የአፋር ክልል መስተዳድር ባለፈዉ ሮብ ባወጣዉ መግለጫ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጭምር አደረሱት ያለዉን ጥቃት አጥብቆ አዉግዟል።የትግራይ ክልል ተቃዋሚ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ ዛሬ ባወጣዉ መግለጫ ደግሞ «አጥፎ ጠፊ» ያለዉ የትግራይ ክልል ገዢ ፓርቲ ህወሓት፣ ከኤርትራዉ ሻዕቢያ ጋር በመሆን ጦርነት አዉጀዋል ብሏል