የአፋር ክልላዊ መንግሥት መስተዳድር «የህወሓት ቡድን» የክልሉን ድንበር ተሻግሮ ጥቃት መፈጸሙን አስታወቀ ። የክልሉ የኮሙኒኬሽን ቢሮ በማኅበራዊ መገናኛ ገጹ ባወጣው መግለጫ የህወሓት ታጣቂዎች የክልሉን ድንበር ተሻግረው በመግባት ስድስት ያህል ቀበሌዎች በቁጥጥራቸው ስር ማድረጋቸውን ገልጿል።