ጦርነቱ በትግራይ ክልል ውስጥ ካስከተለው ሰብአዊ እና ማህባራዊ ቀውስ ባሻገር በአማራ እና አፋር ክልሎችም ተመሳሳይ ውድመት አስከትሏል። በአማራ ክልል በሌላ የግጭት ምዕራፍ የቀጠለው ሰብአዊ ቀውስ ብርቱ ጉዳት እያደረሰ ቢቀጥልም በትግራዩ ጦርነት የደረሰው ጥፋት ግን ለተጎጂዎች ዘላለማዊ ጠባሳ ጥሎ አልፏል።