በመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ላይ የሚደርሱ ጫናዎች እና የተሻሻለው የመገናኛ ብዙኃን ሕግ የሚዲያ ምኅዳሩን "ከፉኛ ይጎዱታል" ሲል የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ገለፀ። የመብት ተሟጋች ድርጅቱ የፕሬስ ነጻነት ቀንን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ የመንግሥት አካላት "ነጻና ገለልተኛ የመገናኛ ብዙኃን እንድኖር ጥበቃና ድጋፍ እንድያደርጉ" ጠይቋል።