የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) በመላው አገሪቱ ዐሥር ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን ዐሳወቀ ፡፡ ኢሕአፓ ዓርብ ሚያዚያ 30 ቀንä 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ፣ መቐለ፣ ባህርዳር፣ ጎንደር፣ ሀዋሳ፣ አሶሳ፣ አዳማ፣ አምቦ፣ ድሬዳዋ እና ሀረር ከተሞች በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ዜጎች እንዲታደሙ ሲል በመግለጫው ጠይቋልም፡፡