በደቡብ እና ሰሜን ወሎ መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ከ64 ሺህ በላይ የሀገር ዉስጥ ተፈናቃዮች በሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ላይ ያላቸው ተሳትፎ በሁለት ተቃራኒ ስሜቶች የታጀበ ሆኗል። ወደ ቀድሞ ሰላማዊ ሕይወታቸው ለመመለስ ተስፋ የሰነቁ እንዳሉ ሁሉ ከድምፅ መስጠት ይልቅ የዕለት ጉርስ እና የመጠለያ ጥያቄ ሲሉ ቅሬታ ያሰሙም አሉ ።