የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ለሚያዚያ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም. በተናጥል በ10 ከተሞች ጠርቶ የነበረውን የአደባባይ ሰልፍ መሰረዙን ዐሳወቀ፡፡ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነትን ከመሰረቱ አራት የፖለቲካ ድርጅቶች አንዱ የሆነው ኢሕአፓ ሰልፉ እንደትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ቅንጅት ወደፊት ቀኑ ተለይቶ እንደሚጠራም ነው ያሳወቀው፡፡