የነዳጅ እጥረቱ በአማራ ክልል በርካቶችን ለኑሮ መመሰቃቀል ዳርጓል ተባለ

Wait 5 sec.

በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰተው የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ መዳረጉ ተገለጸ። አሽከርካሪዎች፣ ከሁለት ሳምንት እስከ አንድ ወር ለሚደርስ ጊዜ ስራ በማቆማቸው ለቤት ኪራይና ለዕለት ጉርስ መቸገራቸውን ተናግረዋል።