ግብፅና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶችም የአሥመራና የአዲስ አበባን መሪዎች በመደገፍ ጠቡን እያባባሱት መሆናቸዉ እየተነገረ ነዉ።የአፍሪቃና የመካከለኛዉ ምሥራቅ ጉዳይ የፖለቲካ ተንታኝ አብዱረሕማን ሰይድ እንደሚሉት የአዲስ አበባና የአሥመራ መሪዎች ባሕሪም ልዩነቶችን በድርድር ለማስወገድ የሚመች አይመስልም