የደሞዝ እና ሌሎች ጥያቄዎችን ያነሱ የትግራይ ሐይሎች አባላት ዛሬ በመቐለ የተቃውሞ ትዕይንት እያደረጉ ይገኛሉ። ዛሬ ረፋድ ጀምሮ ከከማው መሀል ወደ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ የሚወስደውን መንገድ ጨምሮ በርካታ የመቐለ ከተማ ጎዳናዎች በእነዚህ ተቃውሞ እያሰሙ ባሉ የሠራዊት አባላት ተዘግተዋል።