በካርቱም ከተማ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት እና የተናፈቀው የተኩስ አቁም

Wait 5 sec.

የሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም፣ አትባራ እና ኦምዱርማን ላይ ዛሬ አርብ በድሮኖች ጥቃት መፈጸሙን የዐይን እማኞች እና ወታደራዊ መኮንኖች አስታውቀዋል። ጥቃቶቹ የተፈጸሙት አሜሪካን ጨምሮ አራት ሀገራት ብሔራዊ ጦር እና በፈጥኖ ደራሹ ኃይል ለሰብአዊነት ተኩስ እንዲያቆሙ ግፊት እያደረጉ በሚገኝበት ወቅት ነው።