እንግሊዝ ፣ ፈረንሳይ እና ጃፓን የሚገኙበት 28 ሃገራት በጋዛ ሰርጥ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጠበቅ ያለ ጥሪ አስተላለፉ ። ሃገራቱ በጋራ ባወጡት መግለጫቸው በሰርጡ እስራኤል ሲቪሊያውያንን ሳትለይ በምትወስደው ርምጃ በሰርጡ እጅግ የከፋ ሰብአዊ ቀውስ ማስከተሉን ተከትሎ በአፋጣኝ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጠይቀዋል