የኢራን ጦርነት ዓለም አቀፍ ንግድን እያስተጓጎለ ነው። የንግድ መርከቦች ከሱዌዝ ቦይ ይልቅ አፍሪካ ወደሚገኘው ኬፕ ኦፍ ጉድ ሆፕ ለመሄድ ይገደዳሉ። ይህም ወጪን ይጨምራል፤በነዳጅ እና በሌሎች ሸቀጦች የዋጋ ጭማሪ ያስከትላል። ጦርነቱ በውጭ አገር ተቀጥረው ለሚሠሩ አፍሪቃውያንም የኢኮኖሚ መዘዝ አለው።