የዩናይትድ ስቴትስና የእስራኤል ጥቃትም ሆነ ኢራን በባህረ ሰላጤው አገራት ውስጥ በሚገኙ የዋሽንግተን ወታደራዊ ይዞታዎችና ሌሎች ኢላማዎች ላይ እየወሰደች ያለችው የአጸፋ ጥቃት፣በአገራቱ የሚገኙ አፍሪካውያን ዜጎችን ደህንነት አሳሳቢ አድርጎታል።ከዚህ ጦርነት ጋር የተያያዘ ጥቃት ያረፈበት ኢላማ ግን እስካሁን በአፍሪካ ውስጥ አልታየም።