የትግራይ ክልልን ፖለቲካዊ ውጥረት «አሳሳቢ» ያሉ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ተቋማትና ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለችግሩ ሰላማዊ እና ፖለቲካዊ መፍትሔ እንዲሰጥ ጠየቁ። ባይቶናና ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች ደግሞ የክልሉን ችግሮች ለመፍታት አዲስ የሽግግር አስተዳደር መቋቋም አለበት ፤ይህ ካልሆነ ሰላምን ማረጋገጥም ወቅታዊ ችግሮችን መፍታትም አይቻልም ብለዋል።