ሒውማን ራይትስ ዎች፦ «ዶይቸ ቬለ ላይ የደረሰው ጥቃት ገለልተኛው ፕሬስ ላይ የተደቀነ መጠነ ሰፊ ሥጋት ነው» አለ

Wait 5 sec.

ሒውማን ራይትስ ዎች፦ የዶይቸ ቬለ ሁለት ወኪሎች በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለ ሥልጣን ለዘለቄታው መታገዳቸውን አወገዘ ። ለ«ኢትዮጵያ መንግሥት» ጥሪ ያስተላለፈው ሒውማን ራይትስ ዎች፦ «በዶይቸ ቬለ ጋዜጠኞች ላይ የጣለውን እገዳ በአስቸኳይ እንዲያነሳ፤ በመገናኛ ብዙኃን ላይ የሚያደርሰውን ተጨማሪ ጥቃት እንዲያቆም» ሲልም ጥሪ አስተላልፏል ።