ከ5ሺህ በላይ ይሆናሉ የተባሉ ኢትዮጵያውያን ድንገት ወደሀገራቸው እንዲሚመለሱ ተነግሯቸዋል። ኢትዮጵያውንንም ተጠቃሚ ያደርግ የነበረው ቋሚ የመኖሪያና የስራ ፈቃድ የሚያስገኘው የDV መርሃ-ግብር መቋረጡ ተነግሯል። እነዚህ ስደተኞችን የሚያዋክቡ አሰራሮች ወደ አውሮጳ ኅብረት አባል ሀገራትና ብሪታንያም ጭምር የመዛመታቸው አዝማሚያ ያሰጋል።