ኢትዮጵያ ከ10 ዓመታት በፊት ከግል ባለወረቶች አንድ ቢሊዮን ዶላር የተበደረችበት ቦንድ ባለቤቶች እና የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ፓሪስ ዉስጥ ውይይት ጀምረዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት ከግል አበዳሪዎቹ ጋር የሚደረገውን ድርድር ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የተራዘመ የብድር አቅርቦት አራተኛ ግምገማ በፊት የማጠናቀቅ ዕቅድ አለው።