በመካከለኛው ምስራቅ ካለው አለመረጋጋት ጋር ተያይዞ የመጣው የነዳጅ አቅርቦት እጥረት በአማራ ክልል በሚገኙ ከተሞች የትራንስፖርት እንቅስቃሴን ክፉኛ እየፈተነው ይገኛል። በተለይም የኢድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመጓዝ የወጡ በርካታ መንገደኞች በመናኸሪያዎች ተስተጓጉለዉ እንደሚገኙ ታውቋል።