የኢንቨስትመንት ኮሚሽን የ2016 በጀት ዓመት 227 የውጭ ሀገር ባለሀብቶችን ያካተተ በአጠቃላይ 329 አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን ዋና ኮሚሽነር ሃና አርአያ ሥላሴ አመለከቱ። ከአማራ፣ ከኦሮምያ እና ከድሬደዋ ፕሬዝደንት ጽሕፈት ቤቶች ጋር ለውጭ መዋዕለ ንዋይ ምቹ እና የተለየ ጥበቃ ለማመቻቸት መወያየታቸውንም ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል።